“Be the change you want to see in the world.”

አሻራዬ መነቃቂያ ገፅ

“Be the change you want to see in the world.”

አሻራዬ መነቃቂያ ገፅ

ሶስት አለሞች አንዲት ነፍስ 

by | Jun 15, 2017 | Guest writer-እንግዳ ጸሃፍት | 5 comments

(በሚስጥረ አደራው)

እንደዛሬ ያለው ቀን ሲገጥመኝ ይህን አስባለው። ሰው በሶስት አለሞች ውስጥ ገባ ወጣ እያለ እድሜውን የሚፈጅ ፍጡር ይመስለኛል። በእያንዳንዱ አለም የምንሰነብትባቸው የግዜ እርዝማኔዎች ቢለያዩም። ከአንዱ አለም ወደ ሌላው እየተዘዋወርን ይህንን እረጅም የህይወት ጉዞ እንለዋለን….
“ይህች አንዲቷ ነፍስ ሶስት አለሞች ለምዳ
እፎይ ብላ አትኖርም አዬ የሰው እዳ”

የመጀመሪያው አለም- ከሰውም ከራሳችንም ሸሽተን የምንሰነብትበት አለም። ይህ አለም ብዙን ግዜ ከእምነት እና ከጥሞና ጋር የሚዋሃድ አለም ነው። በዚህ አለም ብዙ ባንሰነብትም እንደው ከግርግሩ መሸሽ ሲያምረን እፎይ የምንልበት ምናባዊ ስፍራ ነው። ልክ አንድ የፉከራ ዘፈን ላይ እንደሰማሁት ዘፈን “ገለል በልና ገለል አድርጋቸው” አይነት ፍልፍና የዚህ አለም እውነታ ይመስለኛል። ገለል በማለት ገለል የምናደርጋቸው ብዙ የህይወት እውነታዎች አሉ። ከሰው ጋር ብንወያያቸው መልስ የሌላቸው፤ ወደ ውስጣችን ዘልቀን ከራሳችን ጋር ብንወያይ መልስ የማይገኝላቸው፤ አንዳንድ ጥያቄዎች አሉ። ምንም እንኳን እነዚህ ጥያቄዎች ሁሌም በውስጣችን ቢኖሩም፤ ጩኸታቸው ያየለ ቀን፤ ከሁለተኛውም ከሶስተኛው አለም አስሩጠው እዚህ አለም ውስጥ ያሰነብቱናል……

ሁለተኛው አለም- ሰው ከሰው ሸሽቶ ከራሱ ጋር ብቻ መሆን ሲያምረው የሚሰነብትበት አለም ። አንዳንዴ እኮ መስማት ይሰለቻል፤ ውጭ ውጭውን ማየት እጅ እጅ ይላል። መልሶች ሁሉ ተደርድረው ጥያቄው የሚጠፋበት ወቅት አለ፤ ያኔ ነው በሩጫ እያለከለክን ወደዚህ አለም የምንገባው። በዚህ አለም፤ መልስ ሞልቷል፤ የጠፋው ጥያቄ ነው፤ እሱን ፍለጋ ነው የምንዳክረው። ይህ ሁለተኛው አለም፤ ከመጀመሪያውም ከሶስተኛውም አለም በእጅጉ የጠበበ ነው። የግል አለም ለምን ይሰፋል? እንግዳ የማይደፍረው ቤት ለምን ይሰናዳል? ይህ አለም ወደላይ ለማንጋጠጥ እምነቱን ስናጣ፤ ወደ ሰው ለምቅረብ ብርታቱን ስናጣ መቆዘሚያ መደባችንን የምንዘረጋበት ሁለተኛውም ምናባዊ አለም ነው።

ሶስተኛው አለም- ሰው ከራሱም ከፈጣሪውም ሸሽቶ በሰው ግርግር ውስጥ የሚደበቅበት አለም ነው። በዚህ አለም ነው አዘውትረን የምንገኘው። ውክብክብ ያለ፤ ሰው የራሱን ጩኸት አፍኖ የሌላውን ሹክሹክታ የሚያዳምጥበት፤ የብዙሃን አለም ነው። በዚህም አለም ሰዎች ሁሉ ከራሳቸው ሸሽተው በጋርዮች ስርዓት፤ በጋራ እምነትና አስተሳሰብ፤ በጋራ ፍልስፍናና እውነት የሚደነቋቆሩበት፤ ሰፊ አለም ነው። ሰው ከራሱ ጋር ብቻ አኩኩሉ ሲጫወት የሚታየው በዚህ በሶስተኛው አለም ብቻ ነው። በዚህ አለም የጋራ እውነት እንጂ የግል አመለካከት የለም፤ ፍርድ እንጂ መረዳት የለም፤ ጩኸት እንጂ ትርጉም ያለው ንግግር የለም፤ ሳቅ እንጂ ሀሴት የለም። ቢሆንም ግን በሰመመን የሚያኖር ጊዜ ማሳለፊያ አለም ነው፤ መደበኛ መኖሪያችን ነው……
ምንም እንኳን ጓዝና ቀለባችን በሶስተኛው አለም ውስጥ ቢሆንም፤ ግርግሩ ሲሰለቸን፤ የውጭውና የውስጡ ጦርነት ሲግል፤ ወደ ሌሎቹ ሁለት አለሞች ጎራ ማለታችን አይቀርም። እናም አንዲት ነፍስ በሶስት አለሞች ትኖራለች፤ መጓዝ፤ መሄድ የማይሰለቻት የሰው ልጅ ነፍስ…….

Mistre

Mistre

About Mistre I am the founder of this website www.asharaye.net. I enjoy learning and sharing personal development topics and love to entertain thought-provoking ideas. Writing to me is the best way to express my feelings and understandings about life in general. I am not an expert on any of the subject matters shared. I am just an individual with an opinion; therefore, anything I write and share on this platform is my understanding of the topic.

5 Comments

  1. Ashman

    Thanks Mistrye for sharing and inspiring with such blessed articles all the time, i really admire your commitment and courage to share such motivational story with out any reward. however, i would like to ask u that “introspection” where did u put among the three world…coz i often get myself on it.

    Reply
    • Mistre

      I think most of us pretty much have the same patterns. I find myself a lot on the third one as well. But i think the main thing is having the awareness.

      Reply
      • Tariku(tare)

        I what a blessed thinker u r Mistre? I wonder what would u say if you were us and read your posts?…what would you say?
        then I miss some one who was in the second world ..one who was silent and is with himself..that boy..TARIKU..who is..now at the boundary between second and third…this is a cry to remain in that silen zone..what would u say?

        Reply
  2. Huss

    አመሰግናለሁ እይታሽ በጣም ይመቸኛል።

    Reply
  3. Henok

    Hi Mistre, I want to tell you something you are my hero, because your blogs are always taught me something, and when I start reading your blogs my life is changing day by day and please keep writing because I can’t wait any longer to read your blogs, YOU ARE MY REAL HERO!!!!!

    Reply

Submit a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *