“Be the change you want to see in the world.”

አሻራዬ መነቃቂያ ገፅ

“Be the change you want to see in the world.”

አሻራዬ መነቃቂያ ገፅ

“ሰጠኝ” እና “አገኘሁ”

by | Jan 15, 2017 | መነቃቂያ inspiring stories | 2 comments

(በሚስጥረ አደራው)

የድሮ የኢኮኖሚክስ አስተማሪዬ ነበሩ። ስማቸው ለጊዜው ተዘነጋኝ። ነገር ግን ከአመታት በፊት የተናገሩት ነገር ዛሬም ድረስ አይምሮዬ ውስጥ አለ። አንድ  ቀን የመጨረሻውን የሴሚስተሩን ፈተና ከተፈተንን በኋላ ስለ ውጤት ሲመክሩን እንዲህ ነበር ያሉት። “ከተማሪዎች ባህሪ የሚገርመኝ ነገር ቢኖር፤ ውጤታቸው ጥሩ ሲሆን ማለትም ኤ ሲሆን “ኤ አገኘሁኝ” ይላሉ። በአንጻሩ ውጤታቸው መጥፎ ሲሆን ደግሞ ለምሳሌ ሲ ሲያገኙ ፤”ሲ ሰጠኝ” ነው እንጂ የሚሉት ሲ አገኘሁኝ በፍጹም አይሉም” ሲሉ የተሰማቸውን ነገሩን።

ይህ አባባል ከትምህርት ቤት ውጤት በዘለለ ጥልቅ መልዕክት ያለው ነገር ነው። መምህሩ የተናገሩት በሙሉ አንድ መሰረታዊ እውነታ ላይ ያተኮረ ነው ይኸውም ሰዎች ለውድቀታቸው ሃላፊነትን መውሰድ ፈጽሞ እንደሚከብዳቸው ነው። መልካም ውጤት ስናገኝ በጥረታችን እንዳገኘነው ስናምን፤ መጥፎ ውጤትን ስናገኝ ግን ውድቀታችንን በሌሎች ሰዎች ወይም በሁኔታዎች ማሳበብን እንመርጣለን። ለስኬታችን ሃላፊነትን መውሰድ ከቻለን ለምንድን ነው ለውድቀታችን ሀላፊነት መውሰድ የሚሳነን?

በህይወታችን ሀላፊነትን እንደመውሰድ በዚህ ምድር ላይ እኛን ሊያድነን የሚችል ነገር ያለ አይመስለኝም። ነገሮች ሲስተካከሉ እኛ እንዳስተካከልናቸው ካመንን፤ ነገሮች ሲበላሹም እኛ እንዳበላሸናቸው ማመን መቻል አለብን። ምክንያቱም ለስህተቶቻችን ሀላፊነት መውሰድ ካልቻልን፤ የኑሮዋችንን መሪ የሚጨብጡት ሁሌም ሌሎች ሰዎች ይሆናሉ።

“አገኘሁ” የምንልባቸው ጥቂቶች ነገሮች ይኖሩናል፤ እኛን የማያስወቅሱ እና የሚያስከብሩ መልካም ነገሮች እስከሆኑ ድረስ ብቻ። የሚያሳዘንው ግን “ሰጠኝ” የምንላቸው ነገሮች መብዛታቸው ነው። እኛን የሚያስወቅሱ ነገሮችን በሙሉ “አገኘሁኝ” ብለን በፍጹም ሀላፊነትን አንወስድም። ይልቁንም በህይወታችን የማንፈልጋቸውን ነገሮች በሙሉ ሌሎች እንደሰጡን ማመኑ ይቀለናል። ልክ ተማሪዎችን ሲ ሲያገኙ፤ “ሲ አገኘሁኝ” ከማለት ይልቅ  “ሲ ሰጠኝ” ማለት እንደሚቀናቸው ሁሉ።

በ”ሰጠኝ” እና “በአገኘሁ” መካከል ትልቅ የብስለት ልዩነት አለ። ይህ የብስለት መለክያ  “ሀላፊነት መውሰድ” ይባላል። ለህይወታችን ሀላፊነትን ስንውስድ፤ ስኬታችንንም ሆነ ውድቀታችንን “አገኘሁኝ” ነው እንጂ “ተሰጠኝ” አንልም። ሀላፊነት የሚጎደልን ሰው ስንሆን ደግሞ መልካም መልካሙን “አገኘሁኝ”፤ መጥፎ መጥፎውን ደግሞ “ተሰጠኝ” በማለት ከሃላፊነት የሸሸ ኑሮ እንኖራለን።

“ሰጠኝ” ሳይሆን “አገኘሁ” ማለት ይልመድብን።

Mistre

Mistre

About Mistre I am the founder of this website www.asharaye.net. I enjoy learning and sharing personal development topics and love to entertain thought-provoking ideas. Writing to me is the best way to express my feelings and understandings about life in general. I am not an expert on any of the subject matters shared. I am just an individual with an opinion; therefore, anything I write and share on this platform is my understanding of the topic.

2 Comments

  1. Kedir

    You are right. That is true. But always we shouldn’t ”outsource” our mistakes.
    Thanks Mistre.

    Reply
  2. ሂርሲ

    Absolutely dear sister

    Reply

Submit a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *