by Mistre | Jul 28, 2017 | Guest writer-እንግዳ ጸሃፍት
(በሚስጥረ አደራው) ምንም እንኳን ሂሳብ ላይ እምብዛም ብሆንም ካልተረሱኝ ጥቂት የሂሳብ ጥበቦች (መደመርና መቀነስ ናቸው ዋነኞቹ መቼም) ሌላ አይምሮዬ ውስጥ አልላቀቅም ብሎ የቀረው “Asymptote” የሚለው የሂሳብ ጽንሰ ሃሳብ ነው። የያኔው የሂሳብ አስተማሪዬ አቶ ኤሊያስ ለ” Asymptote” የሰጡን አማርኛ ፍቺ በወቅቱ “ጠጌ ጠጌ አይነኬ” የሚል ነበር።...
by Mistre | Jul 24, 2017 | መነቃቂያ inspiring stories
(በሚስጥረ አደራው) የጥበቃ ልኩ ምን ያህል ነው? በተስፋና በከንቱ ጥበቃ መካከል ያለው መስመር ምን ያህል ቀጭን ነው? በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ተስፋ ቢኖርስ? አንዳንድ ነገሮች ላይመጡ ያስጠብቁናል፤ ተስፋ መቁረጥ አልያም መተው፤ ከተስፋ መቁረጥ በተለየ አወንታዊ የሚሆንበት አጋጣሚ የለም? ጎረቤቴ ነው፤ ይህ ሰዓሊ። ሰዓሊ ያልኩት አዘውትሮ ቀለምና ብሩሹን ይዞ ገርበብ ካለው በራፉ ላይ ስለሚቀመጥ ነው። ተመሳሳይ የስዕል ሸራ...
by Mistre | Jul 16, 2017 | Guest writer-እንግዳ ጸሃፍት
(በሚስጥረ አደራው) አገር ሰላም ብዬ ወደ ስራዬ ለመሄድ በጠዋቱ ጉዜዬን ጀምሬያለው። ከሰሞኑን አንድ ወዳጄ የሰጠኝን ብዙ ዘፈን ያለበት ማጫወቻ እያጫወትኩኝ ነበር። ድንገት ከዚህ ቀደም ልብ ብዬ አድምጬው የማላውቀው የተወዳጁ ዘፋኝ የአለማየው እሸቴ ዘፈን መስረቅረቅ ጀመረ። የመጀመሪያውን የዘፈኑን ስንኝ ስሰማ ግን የሆነ ስሜት ጭንቅላቴን መታኝ፤ ስንኙ እንዲህ ይላል “ሴት ያሳደገው ልጅ ከመባል ዘወትር ለማኝ ሆኖ...
by Mistre | Jul 14, 2017 | Guest writer-እንግዳ ጸሃፍት
(በሚስጥረ አደራው) በፐርሽያ (አሁኗ ቱርክ) ጥንታዊ ጽሁፎች ውስጥ ናስረዲን በጣም ታዋቂ ገጸባህሪ ነው። እንደሚባለው ይህ የሱፊ ፈላስፋ ናስረዲን በ13ኛው ክፍለዘመን የነበረ ብልህ መምህር ነበር። በእሱ ስም የሚተረኩ በጣም ብዙ ታሪኮች፤ ቀልዶችና፤ ትምህርት አዘል መልዕክቶች፤ ዛሬም ድረስ ይነገራሉ። ምናልባት ሳስበው ልክ እንደኛ አገር አለቃ ገብርሃና ይመስለኛል። በእኛ ሃገር ብዙ ቀልዶች አለቃ ገብረሃና እንደተናገሯቸው...
by Mistre | Jul 7, 2017 | መነቃቂያ inspiring stories
(በሚስጥረ አደራው) ሰው ሲያደናቅፈው፤ ወይም የሆነ አደጋ ሲደርስበት “እኔን” ማለት በእኛ ማህበረሰብ የተለመደ ነው። ያንን ሰው አወቅነውም አላወቅነውም፤ ለቤተሰባችንም ሆነ ለመንገደኛ “እኔን” ስንል አይምሮዋችን ሁለቴ አስቦ አይደለም። “እኔን” ማለት የለመደብኝ ከእናቴ ነው፤ ሳላውቀው ውስጤ ተዋህዷል መሰለኝ እኔም ሰው ደንቀፍ ሲያደርገው፤ ወይም ሲጋጭ ብቻ...
Recent Comments